የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ  የአፈፃፀም ሽልማት ለላቀ ስራ ማስፈንጠሪያ መሆኑን አቶ ካሳሁን ጎንፋ  ገለፁ

You are currently viewing የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ  የአፈፃፀም ሽልማት ለላቀ ስራ ማስፈንጠሪያ መሆኑን አቶ ካሳሁን ጎንፋ  ገለፁ

‎AMN ሐምሌ 14 /2017

‎የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2017 በጀት አመት የተሻለ አፈጻጸም ላመጣው  ስኬት መሸለሙ ለአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ  አመራሮች ና ሰራተኞች የተሻለ ለመስራት እንደማስፈንጠራያ መሆኑን የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ስራ አስፈፃሚ አቶ ካሳሁን ጎንፋ ተናግረዋል   ።

‎ ሽልማቱ” ወደ ተሻለ ከፍ እንድንልና ሚዲያው ከነበረበት ሁለትና ሦስት እጥፍ እድንሮጥ” የሚያደርግ ማበረታቻ መሆኑን ስራ አስፈፃሚው አፅንኦት ሰጥተውበታል ።

‎ሽልማት በባህሪው ሀላፊነት መሆኑን የገለፁት ስራ አስፈፃሚው፣  የተሻለ እንዲሰራ ማበረታቻው አደራ ጭምር መሆኑን አመላክተዋል።

‎  ይህም  አደራ በይዘት፣በአቀራረብ፣በቴክኖሎጂና በሰው ሀይል የተሻለ ሚዲያ ማድረግና  መዲናዋን የሚመጥኑ መረጃዎች በፍጥነትና በጥራት  ለሕዝብ ተደራሽ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

‎  ከሚዲያው የተሰጠው  አደራ ለመወጣት ያሉትን ፈተናዎች ማሸነፍ እንደሚገባና አዲስ ሚዲያ  ኔትዎርክ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎች ማፍራት እንደሚገባ ተናግረዋል።

‎  አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ከሚዲያዎች ጋር የሚደረጉ ጤናማ ውድድሮች እንዳሉ ሆነው፣ የተቋሙ ሰራተኞች እርስ በእርስ በማወዳደር ጤናማ የስራ ተነሳሽነትእንዲኖር ስለሚያስችል ለዚያ መዘጋጀት እደሚገባ ገልፀዋል፡፡

‎ዘንድሮ እውቅናዎች እንደተቋም መጀመሩን፣ይህንን ወደ ወደ ግለሰቦች በማውረድ ጤናማ ፉክክር በማድረግ ተቋሙን የተሻለ አፈፃፀም እንዲኖር ማስቻል ይገባል ብለዋል።

‎እውቅና ማግኘት ለአዲስ ሚዲያ  ኔትዎርክ ባህሉ መሆኑን፣የተቋሙ መሪ ቃል “የትውልድ ድምፅ”ን  ትውልድ የሚፈልገው በማሳየትና ለትውልድ አሻራ በማስቀመጥ ረገድ ሰርቶ ማሳየት እንደሚገባ አመላክተዋል።

‎በሔለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review