ጣናነሽ -2 ደጀን ከተማ ደረሰች

You are currently viewing ጣናነሽ -2 ደጀን ከተማ ደረሰች

AMN- ሐምሌ 15/2017 ዓ.ም

ጣናነሽ ቁጥር 2 ጀልባ የአባይ በረሀ ጉዞዋን አገባድዳ ደጀን ከተማ መድረሷን የምሥራቅ ጎጃም ዞን አስተዳዳሪ አቶ ኑርልኝ ብርሃኑ ለኤ ኤም ኤን ዲጂታል ሚዲያ ተናግረዋል፡፡

‎ጀልባዋ ደጀን ከተማ ስትደርስ በነዋሪዎች ደማቅ አቀባበል የተደረገላት ሲሆን፣ ለአካባቢው፣ ለክልሉ እና ለሀገራችን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ መነቃቃት ትልቅ አስተዋፅዖ እንደምታበረክት እምነታቸውን ገልፀዋል፡፡

‎በአንድ ጊዜ 188 ሰዎችን የመጫን አቅም ያላት ጣናነሽ-2፣ የመጨረሻ መዳረሻዋ ወደ ሆነው ጣና ሀይቅ ለመድረስ 335 ኪሎ ሜትር ብቻ ቀርቷታል።

ጀልባዋ ጣና ሐይቅ እስከምትደርስ ድረስ በምታልፍባቸው አካባቢዎች ሁሉ ደማቅ አቀባበል እየተደረገላት ይገኛል፡፡

በወንድማገኝ አሰፋ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review