በታይላንድ እና ካምቦዲያ የድንበር ግጭት የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ አሜሪካ ጠየቀች

You are currently viewing በታይላንድ እና ካምቦዲያ የድንበር ግጭት የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ አሜሪካ ጠየቀች

AMN ሐምሌ 20/2017

በሁለቱ ሀገራት መካከል በድንበር አካባቢ በተከሰተው ግጭት ፤ የካምቦዲያ እና የታይላንድ መሪዎችን ማነጋገራቸውን እና ሁለቱም ሀገራት አፋጣኝ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እንደሚፈልጉ ፕሬዚዳንት ትራምፕ መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

ኘሬዝዳንቱ ስኮትላንድን በጎበኙበት ወቅት ነበር በማህበራዊ ድረ-ገፃቸው ላይ ጦርነቱ እንዲቆም እንደሚፈልጉ የገለፁት ፤ ይህ ካልሆነ ከሁለቱም የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ጋር የንግድ ስምምነቶችን እንደማይፈፅሙ አስጠንቅቀዋል።

በታይላንድ እና ካምቦዲያ ድንበር ላይ ያለው ግጭት ከተጀመረ ሶስተኛ ቀኑ መሆኑ ታውቋል።

በደቡብ ምስራቅ እስያ ጎረቤቶች መካከል በተደረገው ግጭት ፤ ከ30 በላይ ሰዎች መገደላቸውን እና ከ130,000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው ተገልጿል ።

በአሜሪካ ዋሽንግተን የሚገኙት የታይላንድ እና የካምቦዲያ ኤምባሲዎች ፤ ግጭቱን የተመለከተ አስተያየት እንዲሰጡ ለቀረበላቸው ጥያቄ ወዲያውኑ ምላሽ አለመስጠታቸው ተዘግቧል ።

በግጭቱ አሁን ላይ አንድ የታይላንድ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ፤ ወደ ጊዜያዊ መጠለያነት የተቀየረ መሆኑን አንድ በጎ ፈቃደኛ ተናግሯል።

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የታይላንድ አምባሳደር ትናንት በፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ እንደተናገሩት ፤ ከሀምሌ ወር አጋማሽ ጀምሮ በታይላንድ ግዛት ውስጥ ወታደሮች በተቀበሩ ፈንጂዎች መቁሰላቸውን አሳውቋል ። ነገር ግን ካምቦዲያ ይህን ጉዳይ ማስተባበሏ ተገልጿል ።

በብርሃኑ ወርቅነህ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review