2ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስርዓተ-ምግብ ጉባኤ ተሳታፊዎች የጥራት መንደርን ጎበኙ

You are currently viewing 2ኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስርዓተ-ምግብ ጉባኤ ተሳታፊዎች የጥራት መንደርን ጎበኙ

‎AMN ሃምሌ 20/2017

2ኛው የተባበሩት መንግሥታት ሥርዓተ-ምግብ ጉባኤ ተሳታፊዎች በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሥር የሚገኘውን የጥራት መንደር በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል።

‎የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ እንዳለው መኮንን ጎብኚዎችን አቀባበቀል በማድረግ እንኳን ደህና መጣችሁ ብለዋል።

‎ሚኒስትር ዴኤታው ለጉብኝቱ ተሳታፊዎች ኢትዮጵያ የምርቶችንና የአግልግሎት ጥራት ማረጋገጥ የሚያስችል አስተማማኝ ብቃት ያላቸውን ተመጋጋቢ የጥራት መሰረተ-ልማቶችን ያቀፈ ግዙፍ የጥራት መንደር ገንብታ ወደ ሥራ ማስገባቷን ገልጸውላቸዋል፡፡

‎በጥራት መንደሩ በሀገር ውስጥ የሚመረቱ፣ ወደ ውጭ ሀገራት የሚላኩ እና ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የተለያዩ ምርቶችን የጥራት ደረጃ የመፈተሽና ተስማሚነት የማረጋገጥ ተግባራት እንዲደሚከናወኑም ለእንዶቹ አብራርተውላቸዋል፡፡

‎አቶ አንዳለው ኢትዮጵያ የሥርዓተ-ምግብ ሽግግር ከማረጋገጥ በተጓዳኝ የምግብ ጥራትና ደህንነት የማረጋገጥ ሥራዎችን በጥራት ማረጋገጫ መሰረተ-ልማትና በዘመናዊ የላብራቶሪ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ እየሰራች መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

‎የስርዓተ-ምግብ ጉባኤ ተሳታፊዎቹ በጥራት መንደር ከሚገኙ የጥራት ማረጋገጫ መሠረተ-ልማት ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅትን፣ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩትን እና የኢትዮጵያ ስነ-ልክ ኢንስቲትዩትን ከጎበኙ በኋላ ባዩት ነገር መደነቃቸውን ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ በፈጣን የለውጥ ጎዳና ላይ መሆኗንም ምስክርነት ሰጥተዋል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review