ሩሲያ እና ዩክሬን የተኩስ አቁም ስምምነት ማድረግ እንዳለባቸዉ ዶናልድ ትራምፕ አሳሰቡ

You are currently viewing ሩሲያ እና ዩክሬን የተኩስ አቁም ስምምነት ማድረግ እንዳለባቸዉ ዶናልድ ትራምፕ አሳሰቡ

AMN-ሐምሌ 22/2017 ዓ.ም

ዶናልድ ትራምፕ፤ ሩሲያ ከሰኞ ጀምሮ በአስር ወይም አስራ ሁለት ቀናት ውስጥ ከዩክሬን ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት እንድታደርግ ቀነ-ገደብ ወስነዋል ።

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ በበኩላቸው ፤ የትራምኘን ጣልቃ ገብነት እጅግ በጣም ጠቃሚ ነው ብለውታል።

ትራምኘ ከሁለት ሳምንት በፊት ፕሬዝዳንት ፑቲንን ፤ በሀምሳ ቀናት ወስጥ ስምምነት ላይ መድረስ እንዳለባቸውና፤ ይህ ካልሆነ ሩሲያ ከባድ ታሪፍ እንደሚጠብቃት ማሳሰባቸው ይታወሳል።

አሁንም በቀነገደቡ ስምምነት ላይ ካልተደረሰ ፤ በሞስኮ ላይ ማዕቀብ እና ሁለተኛ ደረጃ ታሪፎችን ለመጣል ፍላጎት እንዳለው ትራምኘ ተናግረዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል ።

ትራምኘ በስኮትላንድ ከእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬይር ስታርመር ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን ፤ በውይይቱ የፑቲንን ድርጊት እንደማይቀበሉት መግለፃቸው ታውቋል።

ኘሬዝዳንት ፑቲን በጊዜ ቀነ ገደቡ ዙሪያ ምንም አይነት አስተያየት ያልሰጡ ሲሆን ፤ የመጀመርያው የሀምሳ ቀናት ቀነ-ገደብ ይፋ ሲደረግ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ በጣም ከባድ እና ሞስኮ ይህንን ቀነ-ገደብ ለመተንተን ጊዜ ያስፈልጋታል ሲሉ መናገራቸው ይታወቅ ነበር።

በቱርክ አደራዳሪነት በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል የተካሄደው ሶስተኛው ዙር የተኩስ አቁም ውይይት ፤ በሺዎች የሚቆጠሩ የጦር እስረኞችን ለመለዋወጥ ያስቻለ ሲሆን ፤ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ላይ ግን ምንም አይነት የጎላ ለውጥ አለማምጣቱን ቢቢሲ ዘግቧል።

በሩሲያ እና በዪክሬን መካከል ከተደረገው ከሶስት አመት ተኩል አውዳሚ ጦርነት በኋላ ፤ ሁለቱ ወገኖች በአስራ ሁለት ቀናት ውስጥ ጦርነቱን ለማስቆም እንዴት ስምምነት ላይ ሊደርሱ እንደሚችሉ ግልፅ አለመሆኑ ታውቋል።

በብርሃኑ ወርቅነህ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review