በአስከፊ ሁኔታ የሚኖሩ እናቶች በክረምት የበጎ ፍቃደኞች ቤታቸው በመታደሱ እፎይታን እንዳገኙ ገለፁ

You are currently viewing በአስከፊ ሁኔታ የሚኖሩ እናቶች በክረምት የበጎ ፍቃደኞች ቤታቸው በመታደሱ እፎይታን እንዳገኙ ገለፁ

‎AMN – ሐምሌ 23/2017 ዓ .ም

‎በክረምት የበጎ ፍቃደኞች ቤታቸው የታደሰላቸው እናቶች ከነበሩበት አስከፊ ሁኔታ መላቀቃቸውን ገልፀዋል።

‎ቤታቸው ፈራርሶ ጣራያው ዝናብ የሚያስገባ ከመሆኑ ባሻገር፤ በበራቸው ስር ጎርፍ ያስገባ እንደነበር የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ወ/ሮ ዘይነብ ካሊፋ ያስረዳሉ።

‎ወ/ሮ ዘይነብ በእንባ በተሞላ ድምፃቸው ስለነበሩበት ሁኔታ ሲያስረዱ፤ ለዓመታት ከአንድ ልጃቸው ጋር የኖሩት ህይወት አስከፊ መሆኑን ይገልፃሉ።

‎በክፍለ ከተማው የክረምት በጎፍቃደኛ ወጣቶች፣ ባለሀብቶች እና ተቋማትን በማስተባበር እንደ ወ/ሮ ዘይነብ ላሉ እናቶች ቤታቸውን የማደስ ስራ መጀመሩ ተገልጿል።

‎በበጎ ፍቃደኞች ቤታቸው የታደሰላቸው ወ/ሮ ዘይነብ ፣ይህንን በጎ ተግባር የፈፀሙ አካላትን አመስግነዋል።

‎ሌላኛዋ ልዩ እንክብካቤ የሚፈልጉትን ባለቤታቸውን ይዘው ለ50 ዓመታት በደሳሳ ቀበሌ ቤት አስከፊ ህይወትን ሲገፉ እንደቆዩ የተናገሩት ወ/ሮ ፅግነሽ ፀጋሁን፣ ይህ ታሪካቸው በክረምት በጎ ፍቃደኞች ቤት እድሳት በነበር ሊተካ ከጫፍ ደርሷል ይላሉ።

‎የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ታረቀኝ ኤርሚሾ፣ በክፍለ ከተማው የሚገኙ የቀበሌ ቤቶች ለኑሮ ምቹ እንዳልሆኑ ተናግረዋል።

‎ሃላፊው ባለፉት አመታት በሰው ተኮር ልማት የህብረተሰቡን ኑሮ ለማሻሻል በርካታ ስራዎች እንደተሰሩ ገልፀው፣ በዘንድሮው የክረምት በጎ ፍቃድ የ245 አቅመ ደካሞችን ቤት ለማደስ እየሰሩ መሆኑን አሳውቀዋል።

‎ከእነዚህ መካከል የተወሰኑት በግንባታ ሂደት ላይ ሲሆኑ በተቀሩት ደግሞ ነዋሪዎቹ መግባታቸውን ለማውቅ ተችሏል።

‎ በሔለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review