የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ በትግራይ ክልል

You are currently viewing የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ በትግራይ ክልል

‎AMN- ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም

‎”በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሃሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ ያለው የአንድ ጀምበር 700 ሚሊየን ችግኞችን የመትከል መርሐ-ግብር በትግራይ ክልል እየተከናወነ ይገኛል፡፡

‎በክልሉ በፃዕዳ እምባ ወረዳ በይፋ በተጀመረው መርሐ ግብር፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንትን በመወከል የክልሉ እርሻና ገጠር ልማት ቢሮ ኃላፊ እያሱ አብርሃ (ዶ/ር) መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

‎በመልዕክታቸውም የተፈጥሮ ሃብትን ማዕከል ያደረገ እርሻ ለመፍጠር፣ የአረንጓዴ ልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

‎ለዘላቂ ልማት ተፈጥሮን መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፤ በዛሬው የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብርም በክልሉ ችግኞች እየተተከሉ ነው ብለዋል፡፡

‎የቢሮ ኃላፊው አያይዘውም የተተከሉ ችግኞችን በዘላቂነት መንከባከብ ይገባል ብለዋል፡፡

‎የመርሐ ግብሩ የተሳተፉ ነዋሪዎች ችግኝ መትከል እርጥበትን ለመያዝ፣ ምርታማነትን ለማሳደግ እና የአየር መዛባትን ለመከላከል እንደሚያግዝ ገልጸው፤ የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ በቀጣይም መንከባከብ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review