የተመረቁት ፕሮጀክቶች አራት ኪሎን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የአዲስ አበባ አካባቢዎች የሚያስተሳስሩ መሆናቸዉን ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ ገለጹ

You are currently viewing የተመረቁት ፕሮጀክቶች አራት ኪሎን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የአዲስ አበባ አካባቢዎች የሚያስተሳስሩ መሆናቸዉን ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ ገለጹ
  • Post category:ልማት

AMN ሃምሌ 25/2017

ዛሬ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት የተደረጉት የአራት ኪሎ የገበያ ማዕከላት፣ የመኪና ማቆሚያዎች እና ፕላዛዎች ለህዝባችን የላቀ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ያላቸው መሆናቸዉን ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ ገልጸዋል፡፡

ምክትል ከንቲባ ጃንጥራር አባይ እነዚህ መሰረተ ልማቶች የአከባቢውን ታሪካዊ ይዘትን ያማከሉ ፣ አራት ኪሎን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የአዲስ አበባ አካባቢዎች የሚያስተሳስሩ ናቸዉ ማለታቸዉን ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review