ብቃቴን ለማሳደግ ማንችስተር ዩያይትድ ትክክለኛው ቦታ ነው ፦ ቤንጃሚን ሼሽኮ

You are currently viewing ብቃቴን ለማሳደግ ማንችስተር ዩያይትድ ትክክለኛው ቦታ ነው ፦ ቤንጃሚን ሼሽኮ

AMN- ነሃሴ 3/2017 ዓ.ም

የማንችስተር ዩናይትዱ አዲሱ ፈራሚ ክለቡን በመቀላቀሉ ደስተኛ እንደሆነ ተናግሯል ።

የ22 ዓመቱ አጥቂ ” የማንችስተር ዩናይትድ ታሪክ የገዘፈ እንደሆነ ይታወቃል ፤ እኔን የገዛኝ የወደፊት እቅዱ ነው ።” ሲል ተናግሯል።

ያለኝን ብቃት ለማሳደግ እና ምኞቴን ለማሳካት ዩናይትድ ትክክለኛው ቦታ ነው ያለው ሼሽኮ መለያውን አጥልቆ ወደ ሜዳ እስከሚገባ መቸኮሉን ገልጿል ።

ፉትቦል ዳይሬክተሩ ጄሰን ዊልኮክስ “ሼሽኮ ዓለም ላይ ካሉ ድንቅ ወጣት ባለተሰጥኦዎች አንዱ ነው ። እርሱን በጥብቅ ስንከታተለው ነበር ፤ በክትትላችን በዩናይትድ ሊሳካለት የሚያስችል አቅም እንዳለው አይተናል ። ” ሲሉ ተናግረዋል ።

ቤንጃሚን ሼሽኮ በጀርመኑ ክለብ ላይብዚግ የሁለት ዓመት ቆይታው 39 ግቦችን አስቆጥሯል ።

የግብ መጠኑ በአምስቱ ታላላቅ የአውሮፓ ሊጎች ዕድሜያቸው ከ23 ዓመት በታች ከሆኑ ተጫዋቾች በርካታ ግብ ያስቆጠረ ቀዳሚው ተጫዋች ያደርገዋል ።

በሸዋንግዛው ግርማ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review