ቪክቶር ዮኬሬሽ ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ አርሰናል ድል ቀንቶታል

You are currently viewing ቪክቶር ዮኬሬሽ ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ አርሰናል ድል ቀንቶታል

AMN- ነሃሴ 3/2017 ዓ.ም

አርሰናል ከአትሌቲክ ቢልባኦ ጋር ያደረገውን የኤምሬትስ ካፕ ጨዋታ አሸንፏል።

የሰሜን ለንደኑ ክለብ 3ለ0 ባሸነፈበት ጨዋታ አዲስ ፈራሚው አጥቂ ቪክቶር ዮኬሬሽ ለክለቡ የመጀመሪያውን ግብ አስቆጥሯል ።

ቡካዮ ሳካ እና ካይ ሃቨርትዝ ሌሎቹን ግቦች በስማቸው አስመዝግበዋል ።

መድፈኞቹ በስፖንሰራቸው ኤምሬትስ አማካኝነት ክለቦችን እየጋበዙ በየዓመቱ በሜዳቸው የሚያዘጋጁት ጨዋታ ዘንድሮ ለ14ኛ ጊዜ ተከናውኗል።

ኤምሬትስ ካፕን አርሰናል ዘጠኝ ጊዜ በማሸነፍ የበላይ ነው ።

አርሰናል የፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታውን ቀጣይ ሳምንት እሁድ ወደ ኦልድትራፎርድ በማቅናት ያከናውናል ።

በሸዋንግዛው ግርማ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review