ክሪስታል ፓላስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ

You are currently viewing ክሪስታል ፓላስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ

AMN- ነሃሴ 4/2017 ዓ.ም

ክሪስታል ፓላስ ሊቨርፑልን በመለያ ምት በማሸነፍ የኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫ ባለድል ሆኗል ።

በጨዋታው የ22 ዓመቱ ፈረንሳዊ አጥቂ ሁጎ ኢኪቲኬ በግሩም አጨራረስ ያስቆጠረው ግብ ሊቨርፑልን መሪ አድርጓል ።

የኤፍ ኤ ካፕ አሸናፊው ፓላስ ዦን ፍሊፕ ማቴታ ባስቆጠረው የፍፁም ቅጣት ምት አቻ መሆን ችሏል ።

ሊቨርፑል ብዙም ሳይቆዩ በጀርሚ ፍሪምፖንግ ግብ መሪነታቸውን መልሰዋል ።

በሁለተኛው አጋማሽ ብልጫ የወሰዱት ፓላሶች ግን ኢስማኤላ ሳር ባስቆጠረው ግብ በድጋሚ አቻ ሆነዋል ።

መደበኛው 90 ደቂቃ 2ለ2 ተጠናቆ በተሰጠ መለያ ምት ክሪስታል ፓላስ 3ለ2 አሸንፎ ባለድል ሆኗል ።

በመኪና አደጋ ሕይወቱን ያጣው ዲያጎ ጆታ በታሰበበት ጨዋታ ፓላስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫ ባለቤት ሆኗል ።

በሸዋንግዛው ግርማ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review