ኤቨርተን ጃክ ግሪሊሽን ለማስፈረም ተስማማ

You are currently viewing ኤቨርተን ጃክ ግሪሊሽን ለማስፈረም ተስማማ

AMN- ነሃሴ 5/2017 ዓ.ም

ማንችስተር ሲቲ ጃክ ግሪሊሽን ለኤቨርተን በውሰት ለመስጠት ተስማምቷል ።

የ30 ዓመቱ እንግሊዛዊ በፔፕ ጋርዲዮላ ተመራጭ አለመሆኑን ተከትሎ ክለቡን ለመልቀቅ ተቃርቧል ።

ለክለቡ ክብረ ወሰን የሆነው 100 ሚሊየን ፓውንድ ወጥቶበት ከአስቶንቪላ ሲቲን የተቀላቀለው ግሪሊሽ በኤቨርተን ውሉን ቋሚ የማድረግ አማራጭም አለው ።

በቀጣይ 24 ሰዓትም ዝውውሩን እንደሚያጠናቅቅ ቢቢሲ ስፖርት ዘግቧል ።

ግሪሊሽ በማንችስተር ሲቲ የአራት ዓመት ቆይታው ሰባት ዋንጫዎችን ማሸነፍ ችሏል።

በሸዋንግዛው ግርማ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review