ኢትዮጵያና አሜሪካ ሕገ ወጥ የገንዘብ ማስተላለፊያ መንገዶችን መቆጣጠር በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ መከሩ

You are currently viewing ኢትዮጵያና አሜሪካ ሕገ ወጥ የገንዘብ ማስተላለፊያ መንገዶችን መቆጣጠር በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ መከሩ

AMN ነሐሴ 5/ 2017

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ በኢትዮጵያ ከአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ጋር ሕገ ወጥ የገንዘብ ማስተላለፊያ መንገዶችን መቆጣጠር በሚቻልበት ሁኔታ

መክረዋል።

ሁለቱ ሃገራት በገንዘብ ማስተላለፊያ መንገዶች ላይ በሚደረገው ቁጥጥር ያላቸውን ትብብር ለማጠናከርና የገንዘብ ዝውውሩ በመደበኛ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ መከናወኑን ማረጋገጥ በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ተነጋግረዋል።

በኢትዮጵያ ያለውን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ይበልጥ ማሻሻል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም ከባንኩ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review