ሊቨርፑል አዲሱን የውድድር ዓመት በድል ጀመረ

You are currently viewing ሊቨርፑል አዲሱን የውድድር ዓመት በድል ጀመረ

AMN – ነሃሴ 09/2017 ዓ.ም

የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የ2025/26 የውድድር ዓመት ዛሬ ምሽት በአንፊልድ ሲጀመር ባለሜዳው ሊቨርፑል ቦርንማውዝን 4ለ2 አሸንፏል ።

ከጨዋታው በፊት ሐምሌ ወር ላይ በመኪና አደጋ ሕይወቱ ላለፈው ዲያጎ ጆታ እና ወንድሙ አንድሬ የህሊና ፀሎት ተደርጓል ።

የሊቨርፑል ደጋፊዎችም በልዩ ስሜት ዘክረውታል ።

ለሊቨርፑል የማሸነፊያ ግቦቹን ሁጎ ኢኪቲኬ ፣ ኮዲ ጋክፖ ፣ ፌድሪኮ ኪዬሳ እና ሞሀመድ ሳላህ አስቆጥረዋል ። ሳላህ በመክፈቻ ጨዋታ ያስቆጠራቸውን ግቦች 10 አድርሷል ።

ለቦርንማውዝ ሁለቱንም ግቦች አንቷን ሴሜንዮ ከመረብ አሳርፏል ።

ሊቨርፑል ምንም እንኳን በቦርንማውዝ ቢፈተንም የውድድር ዓመቱን ሦስት ነጥብ በማግኘት ጀምሯል ።

ሸዋንግዛው ግርማ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review