በሲላሲያ ዳይመንድ ሊግ አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ በ1 ሺ 500 ሜትር አሸነፈች

You are currently viewing በሲላሲያ ዳይመንድ ሊግ አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ በ1 ሺ 500 ሜትር አሸነፈች

AMN ነሃሴ 10/2017

የ2025 የዳይመንድ ሊግ የ12ኛ ከተማ ውድድር ዛሬ በፖላንድ ሲላሲያ እየተካሄደ ነው፡፡ ተጠባቂ የነበረውን የ1 ሺ 500 ሜትር ሴቶች ሩጫ አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ አሸንፋለች፡፡

ጉዳፍ አብዛኛውን ዙር ተነጥላ በመውጣት ዋነኛ ተፎካካሪዋን ቢትሪ ቺቤትን በማሸነፍ በአንደኝነት አጠናቃለች፡፡ ውድድሩን ለማሸነፍ ግምት ካገኙ አትሌቶች መካከል የነበረችው ቢትሪስ ቺቤት ሁለተኛ ደረጃን አግኝታለች፡፡

ፍሬወይኒ ኃይሉ አምስተኛ እንዲሁም ብርቄ ኃየሎም ሰባተኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን አጠናቀዋል፡፡

በታምራት አበራ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review