ሞሃመድ ሳላህ የዓመቱ ኮከብ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ

You are currently viewing ሞሃመድ ሳላህ የዓመቱ ኮከብ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ

AMN – ነሃሴ 14/2017 ዓ.ም

የእንግሊዝ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር የ2024/25 የውድድር ዓመት ኮከቦችን ሸልሟል ።

በአዋቂዎች የዓመቱ ምርጥ በሚል ሞሃመድ ሳላህ ተመርጧል ። ሽልማቱን ለሦስት ጊዜ ያሸነፈ ብቸኛው ተጫዋችም ሆኗል።

የ33 ዓመቱ ግብፃዊ በውድድር ዓመቱ በሊጉ ባደረጋቸው 38 ጨዋታ 29 ግብ አስቆጥሮ 18 ወደ ግብነት የተቀየሩ ኳሶችን ማቀበል ችሏል ።

የጎላ ተፅዕኖም ሊቨርፑልን የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን አድርጓል ።

በሴቶች የአርሰናሏ ስፔናዊ አጥቂ ማሪኦና ካልዴንቴ መመረጥ ችላለች ።

በወጣቶች ዘርፍ ከአስቶንቪላ ጋር ድንቅ የውድድር ዓመት ያሳለፈው ሞርጋን ሮጀርስ ተመርጧል ።

በሴቶች ክብረወሰን አሻሽላ ከሊቨርፑል አርሰናልን የተቀላቀለችው ኦሊቪያ ስሚዝ ተሸልማለች ።

የቀድሞ የቼልሲ አሰልጣኝ ኤማ ሃይስ እና ለበርካታ ዓመታት የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድንን የመራው ጋሬት ሳውዝጌት በስፖርቱ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ልዩ ተሸላሚ ሆነዋል ።

የእንግሊዝ ፕሮፌሽናል እግርኳስ ተጫዋቾች ማህበር ያዘጋጀው ሽልማት የዓመቱ ምርጥ ቡድንን መምረጥ ጨምሮ በበርካታ ዘርፎች ሽልማት አበርክቷል ።

የአመቱ ምርጥ ቡድን ውስጥ ሊቨርፑል አራት አርሰናል ሦስት ተጫዋቾችን አስመርጠዋል ።

በሸዋንግዛው ግርማ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review