የኩሙሩክ የወርቅ ፋብሪካ በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ሊሆን እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ

You are currently viewing የኩሙሩክ የወርቅ ፋብሪካ በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ሊሆን እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ

‎AMN ነሀሴ 18/2017 ዓ.ም

የኩሙሩክ የወርቅ ፋብሪካ በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ሊሆን እንደሚችል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

የኩሙርክ ወርቅ ፋብሪካ በ‎ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኝ ሲሆን 20ኪሎ ሜትር የመሬት ስፋት የያዘ ነዉ።

በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ እንደሆነ የተነገረለት ይህ የወርቅ ፋብሪካ በሚቀጥለው አመት ስራ እንደሚጀምር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልፀዋል።

‎ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኩሙሩክ የወርቅ ፋብሪካ እና የአሶሳ ከተማ የኮሪደር ልማት የደረሰበትን ደረጃ የተመለከቱ ሲሆን፣ የወርቅ ፋብሪካዉ በምስራቅ አፍሪካ ትልቁ ፋብሪካ ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።

‎ክልሉ ሰፊ የወርቅ አቅም እንዳለው የሚያሳይ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከባለፈው አመት ጉብኝታችን በኋላ ያየነው እድገት የሚበረታታ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል።

‎ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ በሚጠናቀቅበት ጊዜ በጎ ተጽዕኖው በመላው ክልሉ እንደሚታይ ገልፀዋል፡፡

መሰል ስራዎች ከሌሎች ፕሮጀክቶች ጋር ተደምረው የሀገራዊ ብልጽግናችን መገንቢያ ጡቦች ናቸው ብለዋል።

‎ማዕድን በብዝኃ ዘርፍ የልማት ምልከታችን አንዱ ቁልፍ ዘርፍ ሆኖ ይቀጥላል ሲሉም ተናግረዋል።

‎በፋብሪካው በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን የያዙ መጠለያዎች መኖራቸውን የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ እጅግ ዘመናዊ ፋብሪካ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

‎የኩሙሩክ ወርቅ ፋብሪካ በሚቀጥለው አመት አጋማሽ በኋላ ወደ ምርት እንደሚገባ ጠቁመው፤ ከዚያኛው አመት በኋላ የሚመረተው ወርቅ በአመት እስከ አንድ ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚያስገኝ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስረድተዋል።

‎የኮሪደር ልማቱንም አስመልክተዉ፤ ዛሬ በከተማዋ ያየነው ባለፈው አመት ካየነው በፍፁም ተቃራኒ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

‎የተለወጠበት መንገድ ጥሩ ጅማሮ እንደሆነ የኮሪደር ሥራ ውጤቱ የሚታይ ነው ብለዋል።

በሔለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review