በኢትዮጵያ ስለሚገነባዉ የማዳበሪያ ማምረቻ ፋብሪካ ምን ያህል ያዉቃሉ?

You are currently viewing በኢትዮጵያ ስለሚገነባዉ የማዳበሪያ ማምረቻ ፋብሪካ ምን ያህል ያዉቃሉ?

👉 ፋብሪካዉ በ 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር በጀት ይገነባል

👉 በ40 ወራት ዉስጥ ለማጠናቀቅ ይሰራል

👉 ፋብሪካዉበዓመት ሦስት ሚሊየን ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ የማምረት አቅም አለዉ

👉 የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ የ40 በመቶ ድርሻ አለዉ

👉 የዳንጎቴ ግሩፕ ደግሞ የ60 በመቶ ድርሻ ይኖረዋል

👉 የፋብሪካዉ የማምረት አቅም በዘርፉ ከፍተኛ አምራች ከሆነችው ናይጄሪያ ጋር ተመሳሳይ ነዉ

👉 ፋብሪካዉ ኢትዮጵያ የጀመረችውን የብልጽግና ጉዞ ከሚያረጋግጡ አንኳር ስትራቴጂክ ኢንቨስትመንቶች መካከል አንደኛው ነው

👉 የኢትዮጵያን አርሶአደሮች የረጅም ጊዜ ጥያቄ የሚመልስ ነው

👉 ፋብሪካዉን የሚገነቡት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ እና ዳንጎቴ ግሩፕ ናቸዉ

👉 ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ነዳጅ በመጠቀም የነዳጅ ማስተላለፍያ መስመር ተገንብቶለት ወደ ስራ ይገባል

👉 የዩሪያ ማዳበርያ አንደኛው ግብዓት የተፈጥሮ ነዳጅ ነው

👉 ይህንን ነዳጅ ከካሉብና ሂላላ ሪዘርቭ በመውሰድ ወደ 109 ኪሎሜትር የነዳጅ ማስተላለፍያ መስመር ይገነባል

👉 ይህ የነዳጅ ማስተላለፍያ መስመር ሶማሌ ክልል ጎዴ ድረስ ይደርሳል

👉 ፋብሪካው የሚገነባዉ በጎዴ ነዉ

👉 የተፈጥሮ ጋዙ ለሌሎች ግብዓት መሆን ይችላል

👉 ከፋብሪካ በተጨማሪ በጎዴ የኢትዮጵያን የፔትሮኬሚካል ኢንዱስትሪ ለማቋቋም እቅድ ተይዟ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review