ሃይለማርያም ኪሮስ የሲድኒ ማራቶን አሸናፊ ሆነ

You are currently viewing ሃይለማርያም ኪሮስ የሲድኒ ማራቶን አሸናፊ ሆነ

AMN ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም

ሃይለማሪያም ኪሮስ የሲድኒ ማራቶንን ያሸነፈ ሁለተኛው ኢትዮጵያዊ ሆኗል።

ሃይለማርያም ርቀቱን ለማጠናቀቅ 2:06:06 ሰዓት ፈጅቶበታል። ሰዓቱ በአውስትራሊያ የተመዘገበ ፈጣኑ ሰዓት እንደሆነ ተነግሯል።

ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አዲሱ ጎበና 2:06:16 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ ሆኖ አጠናቋል።

የሴቶቹን ውድድር ሲፈን ሃሰን በቀዳሚነት ጨርሳለች። ኔዘርላንዳዊቷ አትሌት በአውስትራሊያ ፈጣን የተባለውን 2:18:22 ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፋለች።

በሸዋንግዛው ግርማ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review