ኮሚሽኑ መጪዉ ቅዳሜ በካናዳ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አጀንዳ ያሰባስባል

You are currently viewing ኮሚሽኑ መጪዉ ቅዳሜ በካናዳ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አጀንዳ ያሰባስባል
  • Post category:ፖለቲካ

AMN ነሀሴ 27/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በመጪው ቅዳሜ ሴፕቴምበር 6/2025 ወይም ጳጉሜን 1/2017 ዓ.ም በካናዳ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አጀንዳ የሚያሰባስብበት መድረክ እንደሚያካሄድ አስታወቀ።

ኮሚሽኑ በአካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አጀንዳቸውን እያደራጁ እንዲጠብቁ ከወዲሁ ጥሪዉን አቅርቧል።

ሰፕቴምበር 6/2025 በካናዳ ቶሮንቶ በሚካሄደው በዚህ መድረክ በአካባቢው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ እንዲሳተፉ ጥሪ ማቅረቡን ለአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በላከዉ መረጃ አስታዉቋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review