የተለያዩ አገራት መሪዎች እና ልዑካን አዲስ አበባ እየገቡ ነው

You are currently viewing የተለያዩ አገራት መሪዎች እና ልዑካን አዲስ አበባ እየገቡ ነው

AMN ጳጉሜ 2 ቀን 2017

የጋምቢያ ምክትል ፕሬዝዳንት ሞሃመድ ጃሎ እና የጅቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ሁሴን አብዱልቃድር ፣ የጋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሙኤል ኦኩዴዜቶ አብላክዋ በአፍሪካ-ካረቢያን ማህበረሰብ ጉባኤ እና በአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል ።

በቦሌ አለምአቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የሰላም ሚኒስትር አቶ መሀመድ እድሪስ እና ሌሎች ከፍተኛ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል ማድረጋቸዉን ከዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review