‎የአሸናፊነታችን፣ የመቻላችን ሚስጥር ህብረብሄራዊ አንድነታችን ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ባህልና ኪነ-ጥበብ ቢሮ ኃላፊ ሂሩት ካሳው (ዶ/ር) ተናገሩ

You are currently viewing ‎የአሸናፊነታችን፣ የመቻላችን ሚስጥር ህብረብሄራዊ አንድነታችን ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ባህልና ኪነ-ጥበብ ቢሮ ኃላፊ ሂሩት ካሳው (ዶ/ር) ተናገሩ

‎AMN ጳጉሜን 2/2017 ዓ.ም

‎‎የአሸናፊነታችን፣ የመቻላችን ሚስጥር ህብረብሄራዊ አንድነታችን ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ባህልና ኪነ-ጥበብ ቢሮ ኃላፊ ሂሩት ካሳው (ዶ/ር ) ተናግረዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ባህልና ኪነ-ጥበብ ቢሮ አራት ኪሎ ኘላዛ ላይ በተለያዪ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶች የጳጉሜን ሁለት የሕብር ቀንን በድምቀት አክብሯል፡፡

‎የቢሮው ሀላፊ ሂሩት ካሳው (ዶ/ር) በዝግጅቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የጳጉሜን ሁለት የህብር ቀን “ብዘሀነት የኢትዮጰያ ጌጥ” በሚል መሪ ሀሳብ እየተከበረ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

‎የአሸናፊነታችን፣ የመቻላችን ሚስጥር ህብረብሄራዊ አንድነታችን ነው ያሉት ሀላፊዋ፤ ብዝሀነታችን ዛሬም ትናንትም አሸናፊ እንድንሆን አድርጎናል ብለዋል።

‎የህብር ቀንን የምናከብረው በአዲስ አመት ዋዜማ በመሆኑ ህብረታችንን የተሻለ ነገን ለመስራት እንደመንደርደሪያ መጠቀም አለብን ሲሉ ተናግረዋል።

‎የአዲስ አመት መንደርደሪያ የጳጉሜ ወር፤ የተስፋ፣ የይቅርታ እና የሰላም እንዲሆን የምንመኝበት፤ የላቀ ለመስራት የምናቅድበት ነው ብለዋል።

‎የህብር ቀን በአራት ኪሎ እንብርት ላይ በብስክሌት ውድድር፣ በስኩተር እንቅስቃሴዎች ፣ በባህላዊ የበዓልና አገራዊ ሙዚቃዎች፣ ስዕል በመሳል እና በተለያዩ ዝግጅቶች ተካሂዷል።

‎ህብር ቀን የኢትጵያን ህብረብሄራዊ አድነትን በሚገልፅ እና በሚሳይ መንገድ የተከበረ ሲሆን፣ አዲስ አመት ዋዜማን የሚያደምቁ ዝግጅቶች ቀርበዋል።

‎በሔለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review