‘ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ’
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ‘የነገው ቀን’ን በተመለከተ መልዕክት አስተላልፈዋል። ሙሉ መልዕክታቸው ቀጥሎ ቀርቧል።
ትናንትን በመጠቀምና በማረም፣ ዛሬ ላይ ተግተን በመሥራት፣ ነገን እጅግ የተሻለ ለማድረግ ተነሥተናል፡፡ በአናሎግ ዘመን የነበሩ ችግሮች በዲጂታል ዘመን አይደገሙም፡፡ ነገ “ዲጂታል ኢትዮጵያ” ፕሮጀክት ከመሆን አልፎ ባህል ይሆናል፡፡

ንግድ እና አገልግሎታችንን በማቀላጠፍ፣ መረጃዎቻችንን ተደራሽ በማድረግ፣ አንድ ሰው አንድ እንዲሆን በማስቻል፣ የፋይናንስ ሥርዓታችንን ይበልጥ ተደራሽ ቀልጣፋ እንዲሆን በማድረግ፣ የትምህርትና የጤና አገልግሎቶችን በየአቅጣጫው በማስፋፋት፣ ዲጂታል ኢትዮጵያ እንዲሳካ የሁላችንን ጥረትና ትኩረት ይፈልጋል፡፡