ዛሬ በተጀመረው የቶክዮ ዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከሚጠበቁ ውድድሮች አንዱ ሌሊት የሚደረገው የሴቶች ማራቶን ነው፡፡
በዚህም ውድድር የኬንያ እና የኢትዮጵያውያን ፍጥጫ ይጠበቃል፡፡ ሁለቱ ሀገራት በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች ማራቶን ከፍተኛውን ሜዳልያ ማግኘት ችለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በእስካሁን ጉዞዋ 3 ወርቅ ፣ 1 ብር እና 1 ነሃስ ሜዳልያ አግኝታለች ፡፡ ኬንያ 5ወርቅ ፣ 5 ብር እና 1 ነሃስ በማምጣት የበላይነቱን ትወስዳለች፡፡
ኢትዮጵያ በሴቶች ማራቶን ከዚህ ቀደም ሜዳልያ ካስገኙላት አትሌቶች አንዳቸውንም ወደ ቶክዮ ይዛ አልሄደችም፡፡
ትዕግስት አሰፋ ፣ ሱቱሜ አሰፋ እና ትዕግስት ከተማ በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች ናቸው፡፡
በዚህ ውድድር ትዕግስት አሰፋ በትልቁ ትጠበቃለች፡፡ አትሌቷ በ2023 በበርሊን የሮጠችው 2፡11፡53 የዓለም ሁለተኛው ፈጣን ሰዓት ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ሰዓቱ በሩት ቼፕንጌቲች በ1 ደቂቃ 57 ሰከንድ እስኪሻሻል የዓለም ክብረወሰን ነበር፡፡
ትዕግስት ባሳለፍነው ሚያዚያ ወር በሴት አሯሯጮች ብቻ ታግዛ ያስመዘገበችው 2፡15፡50 የዓለም ክብረወሰን ሆኗል፡፡ በውድድሩ ወንድ አሯሯጮች ባለመሳተፋቸው በክብረወሰንነት ተይዟል።
በፓሪስ ኦሊምፒክ የብር ሜዳልያ ያገኘቸው ትዕግስት በዛሬው የሌሊት ውድድር ዋነኛ አላማዋ ለሀገሯ ወርቅ ማምጣት ነው፡፡
2፡15፡55 የግል ምርጥ ሰዓት ያላት ሱቱሜ አሰፋ እንዲሁም 2፡16፡07 የሆነ የግል ምርጥ ሰዓት ያላት ትዕግስት ከተማ ሌሎች ለሜዳልያ የሚሮጡ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ናቸው።
በኬንያ በኩል ፔርስ ጄፕቺርቺር ፣ ጃክሊን ቼሮኖ እና ማግዳልያን ማሳይ ተሳታፊ ይሆናሉ፡፡
ሩጫው ለሊት 8 ሰዓት ላይ ይጀምራል፡፡
በሸዋንግዛው ግርማ
በ10000M በሴቶች በዓለም ከ30 ደቂቃ በታች ያሉትን ይዘን ተሳትፈን ውጤቱን እንዳየነው ነው ጉዳዩ የሰዓት ጉዳይ ሳይሆን የውሳኔና የጽናት ጉዳይ ነው የታክቲክም ጉዳይም ጭምር እንጅ
- 4h
- Reply
AMN-Addis Media Network
sootneSrpdgu342fm5487i270ct9m48t39f4g4u6a0u6m75aft85gi3fih14 ·
የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ የተካሄደ የስፖርት ፌስቲቫልና የጎዳና ላይ ትርዒት፤…
See more

0:00 / 1:57
ህዳሰአችን የደም፣የላብ እና የእንባ ጠብታ አሻራችን ነዉ
- 3h
- Reply
AMN-Addis Media Network
sootneSrpdgu342fm5487i270ct9m48t39f4g4u6a0u6m75aft85gi3fih14 ·
ማርቲን ዙብሜንዲ ሁለት ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ አርሰናል ኖቲንግሃምን አሸነፈ
AMN Sport
sootneSrpdgu342fm5487i270ct9m48t39f4g4u6a0u6m75aft85gi3fih14 ·
ማርቲን ዙብሜንዲ ሁለት ግብ ባስቆጠረበት ጨዋታ አርሰናል ኖቲንግሃምን አሸነፈ…
See more
Giokres yaskoteres
- 4h
- Reply