መንግስት ተቋማት ተናበውና ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር አሳሰቡ

You are currently viewing መንግስት ተቋማት ተናበውና ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር አሳሰቡ

AMN – መስከረም 8/2018 ዓ.ም

ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶችን በ2018 በጀት ዓመት በላቀ ደረጃ ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የመንግስት ተቋማት ተናበውና ተቀናጅተው ሊሰሩ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር አሳሰቡ።

‎የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ2018 በጀት ዓመት እቅድ ግብ ስምምነት ፊርማ መድረክ ተካሄዷል።

‎የከተማዋ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶችን በ2018 በጀት ዓመት በላቀ ደረጃ ውጤታማ ለማድረግ ሁሉም የመንግስት ተቋማት ተናበውና ተቀናጅተው ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።

‎የዘንድሮው የከተማዋ እቅድ የለውጡ መንግስት የ10 አመት የልማት እቅድ አካል የሆነው የመጀመሪያው 5 አመት የመጨረሻው አመት የልማት እቅድ መሆኑን የገለጹት አፈ ጉባኤዋ እቅዱን በተደመረ አቅም በመተግበር ከተማዋን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ በትጋት ልንሰራ ይገባል ብለዋል።

‎በእቅድ ግብ ስምምነት ፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ አባላት የሁሉም የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች እና ተጠሪ ተቋማት ተገኝተዋል።

በምትኩ ተሾመ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review