የመደመር መንግሥት መፅሀፍ የዘመናት ችግሮችን የዳሰሰ እና መፍትሄ አመላካች መሆኑን ሙህራን ገለፁ

You are currently viewing የመደመር መንግሥት መፅሀፍ የዘመናት ችግሮችን የዳሰሰ እና መፍትሄ አመላካች መሆኑን ሙህራን ገለፁ

‎AMN መስከረም 11/2018 ዓ.ም

‎የመደመር መንግሥት መፅሀፍ የዘመናት ችግሮችን የዳሰሰ እና መፍትሄ አመላካች መሆኑን በተለያየ ዘርፍ የተሰማሩ ሙህራን ገልፀዋል።

‎የመደመር መንግሥት መፅሃፍ እሳቤ ላይ ያተኮረ ውይይት በየካ ክፍለ ከተማ ተካሂዷል ።

‎የመደመር መንግሥት እሳቤ በተለያዩ ሙህራን ግንዛቤን የሚፉጥሩ የተለያዩ ሀሳቦች የቀረቡ ሲሆን ሰፊ ውይይትም ተደርጓባቸዋል።

‎የውይይቱ አላማ የመደመር መንግሥት ዕሳቤን በማህበረሰቡ ለማፅረስ መሆኑን የተናገሩት የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ መገርሳ ገላና፤ በቀጣይም ተመሳሳይ መርሃ ግብሮች በክፍለ ከተማው ይቀጥላሉ ብለዋል

‎የውይይቱ ተሳታፊዎቹ የመደመር መንግሥት መፅሀፍ ለቀጣይ ትውልድ መሠረት የሚጥል እና ሀገርን በጋራ ለማሻገር የሚያግዝ መሆኑን መገንዘባቸውን ተናግረዋል

‎የመደመር መንግሥት መፅሀፍ ፍጥነትና ፈጠራን እንዲሁም ክፍተቶችን የማረም አቅም የሚፈጥር መሆኑም በመድረኩ ተመላክቷል።

‎በመርሃ ግብሩ የተለያዩ ሙህራን፣ የሀይማኖት አባቶች፣ አባገዳዎች፣ ፖለቲከኞችና ማህበረሰብ አንቂዎች እንዲሁም በተለያየ ዘርፍ የተሰማሩ ሙህራን ተሳትፈዋል።

‎በመሀመድኑር ዓሊ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review