ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኃይል ማመንጫ፣ ግብርና፣ የጤና ጥበቃ ልማት እና የመከላከያ ትብብርን በተመለከተ ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተወያዩ

You are currently viewing ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የኃይል ማመንጫ፣ ግብርና፣ የጤና ጥበቃ ልማት እና የመከላከያ ትብብርን በተመለከተ ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ተወያዩ

AMN – መስከረም 16/2018 ዓ.ም

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባስለተላፉት መልእክት፤ ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በተለያዩ ዘርፎች ላይ አጠቃላይ ውይይት ማካሄዳቸውን ገልፀዋል፡፡

እነዚህም የኃይል ማመንጫ፣ ግብርና፣ የጤና ጥበቃ ልማት እና የመከላከያ ትብብርን ያካትታሉ ብለዋል።

በተለይም ለማኅበረሰብ አገልግሎት የሚውል ንፁህ ኃይል ለማቅረብ የጋራ የኒኩሊየር ኃይል ማመንጫ ለማልማት ስምምነቶችን በመፈራረም የጋራ ፍላጎቶችን የሚያጎለብቱ ጉዳዮች ላይ መመካከራቸውን ገልፀዋል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review