የሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል በአባ ገዳዎችና ሃደ ሲንቄዎች ምርቃት ተጀምሯል

You are currently viewing የሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል በአባ ገዳዎችና ሃደ ሲንቄዎች ምርቃት ተጀምሯል

AMN – መስከረም 24/2018 ዓ.ም

‎የ2018 የሆረ ፊንፊኔ የኢሬቻ በዓል አከባበር አባ ገዳዎች እና ሀደ ሲንቄዎች ወደ መልካ ከመሄዳቸው በፊት በባህሉ መሰረት አባ ገዳዎች በምርቃት ስነ- ስርዓት በዓሉን አስጀምረዋል፡፡

የዘንድሮው የኢሬቻ በዓል “ኢሬቻ ለሀገር ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ የሚከበር ሲሆን፤ የሆረ ፊንፊኔ የሚከበርባት አዲስ አበባ ከተማ ከዋዜማ ጀምሮ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ደምቃለች።

‎መዲናዋ በዋዜማው በአምስቱም የመግቢያ በሮች በዓሉን ለመታደም የመጡ እንግዶችን በኢትዮጵያዊ እንግዳ አቀባበል ባህል በተለያዩ አካባቢዎች የተቀበለች ሲሆን፣ በምሽት ድባቡም የኢሬቻን በዓል የሚገልፅ የድሮን ትርኢት መቅረቡ ይታወሳል።

‎አባ ገዳዎች እና ሀደ ሲንቄዎችም በዓሉ ወደሚከበርበት ስፍራ በማቅናት ላይ ይገኛሉ፡፡

በሔለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review