ኢሬቻ በኪነ ጥበብ ባለሙያዎች አንደበት

You are currently viewing ኢሬቻ በኪነ ጥበብ ባለሙያዎች አንደበት

AMN – መስከረም 24/2018 ዓ.ም

‎በአፋን ኦሮሞ ከተከታታይ የሬድዮ ድራማ ውስጥ “አባ ጃንቦ” በግንባር ቀደምነት ይጠቀሳል።

‎ለ20 ዓመታት በተከታታይ ለአድማጭ ሲደርስ እንደነበር የሚጠቀሰው አባ ጃንቦ፣ በዚህ ተከታታይ ድራማ ውስጥ ከተሳተፉ እውቅ ተዋንያን የኪነ ጥበብ ባለሙየዎች መካከል አንዷ አርቲስት አበበች አጀማ ናት።

‎አርቲስት አበበች ፣ በሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል ለማክበር ከተገኙ ታዋቂ የኪነ-ጥበብ ሰዎች መካከል አንዷ ናት።

‎በዓሉ ከተሰራው የመሰረተ ልማት ጋር ተዳምሮ ለከተማዋ ልዩ ውበት ከማላበሱ በተጨማሪ ፣ በዓሉን በአንድነት፣ በፍቅር እና በደስታ ማክበራቸውን ተናግራለች።

‎ኢሬቻ ማለት ውሀውን፣ ቄጠማውን እና የተፈጥሮ ሀብትን የፈጠረ አምላክን ከክረምትና ከጭጋጋማው ወቅት ወደ ብራ ስላሸጋገረን የምናመሰግንበት ቀን ነው ብላለች።

‎የኢሬቻን በዓል ከኦሮሞ ተወላጆች በተጨማሪ የተለያዩ ብሄረሰቦች በድምቀት ያከበሩበት ጊዜ መሆኑ አስደሳች ነው ብላለች።

‎የኢሬቻ በዓል አከባበር ከአመት አመት ውበቱ እያማረ እና እየፈካ እንደሚገኝ ምልከታዋን አጋርታለች።

‎በተለይ የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማትን ስትመለከት ውጭ አገር እንደሚመስላት ገልፃ፣ ከተማዋ እንደ ስሟ አዲስ መሆኗ አስደስቶኛል ብላለች።

በሔለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review