በበጀት አመቱ ኢትዮጵያ 8.8 በመቶ ኢኮኖሚያዊ እድገት ማስመዝገቧን ኘሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ስላሴ ገለፁ

You are currently viewing በበጀት አመቱ ኢትዮጵያ 8.8 በመቶ ኢኮኖሚያዊ እድገት ማስመዝገቧን ኘሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ስላሴ ገለፁ

‎AMN – መስከረም 26/2018 ዓ.ም

‎6ኛው የሕዝብ ተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን መክፈቻ ስነ- ስርዓት በዛሬው ዕለት ተጀምሯል።

‎በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢፌድሪ ኘሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ስላሴ እንደተናገሩት፣ ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት 8.8 በመቶ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ማስመዝገቧን ተናግረዋል።

‎በበጀት ዓመቱ በግብርና ዘርፍ 1.57 ቢሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን የገለፁት ኘሬዝዳንቱ፣ ከ2016 በጀት አመት ጋር ሲነፃፀር የ24.7 በመቶ ብልጫ እንዳለው አመላክተዋል።

‎በኢንዱስትሪ የማምረት አቅም በ2017 በጀት ዓመት ወደ 65 በመቶ ከፍ ማለቱን ገልፀው፣ በ2016 በጀት ዓመት 59 በመቶ ብቻ እንደነበር አስታውሰዋል።

‎በ2017 በጀት አመት ኢትዮጵያ 38.87 ቶን የወርቅ ምርት መገኘቱን አስረድተው፣ ባለፈው አመት ከተገኘው የ3.9 ቶን የወርቅ ምርት በንፅፅር የተገኘውን የምርት ዕድገት ገልፀዋል ። የሲሚንቶ ምርት በ2016 ከነበረው የ7.5 ሚሊዮን ቶን ወደ 9.1 ሚሊዮን ቶን ከፍ ማለቱን ገልፀዋል፡፡

በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ላይ ከተገኙት ተጋባዦች መካከል የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት ተጠሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ታዋቂ ሰዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

‎በሔለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review