በህዝብና በመንግስት መካከል ያለውን መደላድል ለመፍጠር የምክር ቤት አባላት በሀሳብና በተግባር ጥረታቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ቡዜና አልከድር አሳሰቡ

You are currently viewing በህዝብና በመንግስት መካከል ያለውን መደላድል ለመፍጠር የምክር ቤት አባላት በሀሳብና በተግባር ጥረታቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ዋና አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ ቡዜና አልከድር አሳሰቡ

AMN-መስከረም 29/2018

የምክር ቤት አባላት በሀሳብና በተግባር ወደ ህዝቡ በመቅረብ በህዝብና መንግስት መካከል መዳላድልን ለመፍጠር እያደረጉት ያለውን ጥረት አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ዋና አፈ -ጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር ገለፁ::

የካ ክፍለ ከተማን በመወከል የአዲስ አበባ ምክር አባላት የሆኑ ተመራጮች ከመረጣቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት እያካሄዱ ይገኛሉ ።

የምክር ቤቱ አባላት ከመረጣቸው ህዝብ ጋር ውይይት ማድረጋቸው አንዱ የዲሞክራሲ ስርአት ማሳያ ነው ያሉት የአዲስ አበባ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር ይህም የህዝብን ጥያቄ ለመመለስና ዘላቂ መፍትሄን ለመስጠት የሚያስችል ቁልፍ መሳሪያ ነው ብለዋል።

የምክር ቤቱ አባላት ወደ ህዝቡ በመቅረብ የሚያደረጓቸው ውይይቶች የህዝብ ጥያቄዎች እንዲፈቱ በማስቻል ረገድ ትልቅ ሚና እንዳላቸው አንስተዋል ፡፡

ምክር ቤቶች የህዝብ ሉአላዊነት መገለጫ ተቋማት እንደመሆናቸው መጠን የህዝብ የልብ ትርታ ቀርበው በማድመጥ በርካታ የህዝብ ችግሮችንም መፍታት መቻሉም ተጠቁማል።

በውይይቱ ባለፈው በጀት አመት የተከናወኑ ተግባራትና የቀጣይ የቤት ስራዎችን የተመለከተ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

በራሔል አበበ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review