የዘንድሮዉ የኢሬቻ በዓል ” ኢሬቻ ለሃገር ማንሰራራት” በሚል መሪ ቃል በኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በተለያዩ ባህላዊ ክዋኔዎች እየተከበረ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት በቡራዩ ኢሬቻ መልካ አቴቴ በቡራዩ: በሰበታ ኢሬቻ መልካ ሰበታ: በገላን ኢሬቻ መልካ ጨፌ ቱማ: በሰንዳፋ በኬ ኢሬቻ መልካ ጎራ እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢሬቻ መልካ አሶሳ አባገዳዎች: ሃዳ ሲንቄዎች: ቄሮዎች: ቀሬዎች: ፎሌዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በመከበር ላይ ይገኛል።
የኦሮሞ ህዝብ የአንድነት መገለጫ እና የህብረብሄራዊነት ተምሳሌት የሆነዉ የኢሬቻ በዓል ከሆረ ፊንፊኔ እና ከሆረ ሃረሰዴ በመቀጠል በሃገር ዉስጥ እና በዉጭ ሃገራት ጭምር በድምቀት ይከበራል።
በወንድማገኝ አሰፋ