በሁለቱ የባሌ ዞኖች በግብርናው ዘርፍ የተሰራው ስራ ለመላው ኢትዮጰያ የሚተርፍ ምርት የሚገኝበት ነው

You are currently viewing በሁለቱ የባሌ ዞኖች በግብርናው ዘርፍ የተሰራው ስራ ለመላው ኢትዮጰያ የሚተርፍ ምርት የሚገኝበት ነው

‎AMN ጥቅምት 10/2018 ዓ.‎

‎በሁለቱ የባሌ ዞኖች በግብርናው ዘርፍ የተሰራው ስራ ለመላው ኢትዮጰያ የሚተርፍ ምርት የሚገኝበት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ ከፍተኛ አማካሪ

‎አምባሳደር ግርማ ብሩ ገልፀዋል።

‎የሶፍ ኡመር ወግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከቀድሞ እና በስራ ላይ ካሉ አመራሮች ጋር በውቡ ሶፍ ኡመር ዋሻ ውይይት አድርገዋል።

‎ በውይይቱ አምባሳደር ግርማ ብሩ እንደተናገሩት፣ በሁለቱ የባሌ ዞኖች ብቻ 1ሚሊዮን ሄክታር መሬት መታረሱ ገልፀው፣ ምርታማ የሆነው 20 በመቶ እንኳ ቢሆን 20 ሚሊዮን ኩንታል የሚያስገኝ መሆኑን አስረድተዋል።

‎ይህ ምርት ደግሞ ለመላው ኢትዮጵያ የሚተርፍ መሆኑን አስረድተው፣ ይህንን አከባቢ ነበር ተዘንግቶ የቆየው ሲሉ በቁጭት ተናግረዋል።

‎እኔ ባሌን የማውቀው የባሌ ጠቅላይ ግዛት በሚባልበት ወቅት ነው ያሉት አምባሳደሩ ፣ በባለፉት ቀናት በሁለቱ የባሌ ዞኖች በግብርናው ዘርፍ የተሰራው ስራ ለመላው ኢትዮጰያ የሚተርፍ ምርት የሚገኝበት መሆኑን ነው ።

‎በሔለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review