የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በሶስት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ውይይት በማድረግ ውሳኔ አሳልፏል

You are currently viewing የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በሶስት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ውይይት በማድረግ ውሳኔ አሳልፏል

AMN ጥቅምት 12/2018

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 5ኛ ዓመት 4ኛ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው እለት አካሂዷል።

ካቢኔው በዛሬው ውሎው በቀረቡ ሶስት ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ ውይይት በማድረግ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

በዚህ መሰረት፡-

1ኛ. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ፣ የክፍለ ከተማና ወረዳ ምክር ቤት አባላትን ቁጥር ለመወሰን የወጣ አዋጅ ላይ በመወያየት ለምክር ቤት እንዲቀርብ ውሳኔ ማሳለፉ ታውቋል።

2ኛ. የተቋራጭ የግንባታ ግዢና የሥራ ስምሪት የአሰራር ደንብ ቁጥር ……. /2018 ላይ ተወያይቶ ወሳኔ አሳልፏል፡፡

3ኛ. ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸዉ ፕሮጀክቶች የመሬት ጥያቄ ላይ ውይይት በማድረግ ውሳኔ ማሳለፉን ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review