ስልክ ቀምቶ የቆሻሻ ማስወገጃ ቱቦ ውስጥ በመግባት ሊያመልጥ የነበረ ተጠርጣሪ ከ5 ሰዓታት ቆይታ በኋላ ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ዋለ

You are currently viewing ስልክ ቀምቶ የቆሻሻ ማስወገጃ ቱቦ ውስጥ በመግባት ሊያመልጥ የነበረ ተጠርጣሪ ከ5 ሰዓታት ቆይታ በኋላ ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ዋለ

AMN ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ/ም

ከአንድ ግለሰብ ስልክ ቀምቶ የቆሻሻ ማስወገጃ ቱቦ ውስጥ በመግባት ሊያመልጥ የነበረ ተጠርጣሪ ከ5 ሰዓታት ቆይታ በኋላ ከነ ኤግዚቢቱ መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገለጸ።

ተጠርጣሪው የቅሚያ ወንጀሉን ፈጽሞ የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ቱቦ ውስጥ በመግባት ሊያመልጥ ሲል በቁጥጥር ስር የዋለው ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ/ም በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 5 አቤቤ ሱቅ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ነው።

ተጠርጣሪው የግል ተበዳይ ከባንክ ብር አውጥተው ሲወጡ ጠብቆ የዋጋ ግምቱ 120 ሺ ብር የሚያወጣ sumsung altra si25 ስማርት ስልክ በመንጠቅ በአካባቢው ወደሚገኝ የቆሻሻ ማስወገጃ ቱቦ ውስጥ ገብቷል።

የወንጀል ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላ የግል ተበዳይ የይድረሱልኝ ጥሪ በማሠማታቸው የአካባቢው ህብረተሰብ እና ፖሊስ ወዲያው ቦታው ላይ በመድረስ ተጠርጣሪው በገባበት የፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ቱቦ ውስጥ ተከታትሎ በመግባት ሊያወጡት መቻላቸውን የየካ ክፍለ ከተ ማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

ተጠርጣሪው ከቱቦው ውስጥ ሲወጣ ስልኩን ትቶ የወጣ ቢሆንም ፖሊስ ተጠርጣሪውን በድጋሚ ወደ ቱቦው ውስጥ ይዞ በመግባት ስልኩን ከጣለበት ውሃ ውስጥ እንዲያወጣው ማደረጉን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።

በእንደዚህ ዓይነት የወንጀል ተግባር ላይ የሚሰማሩ ወንጀል ፈጻሚዎች ከህግ እንደማያመልጡ አውቀው ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ለኤኤምኤን በላከዉ መረጃ አሳስቧል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review