ጥናቶች እና የምርምር ስራዎች ሳይንሳዊና በእውቀት ላይ የተመሰረቱ መሆን አለባቸው

You are currently viewing ጥናቶች እና የምርምር ስራዎች ሳይንሳዊና በእውቀት ላይ የተመሰረቱ መሆን አለባቸው

‎AMN .ጥቅምት 22/2018 ዓ.ም

‎ጥናቶች እና የምርምር ስራዎች ሳይንሳዊና በእውቀት ላይ የተመሰረቱ መሆን አንዳለባቸው የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ገለፀ ።

የ‎ኢንስቲትዩቱ የምርምር ስራዎች ሳይንሳዊና በእውቀት የተመሰረቱ እንዲሆኑ እና የጥናት እና የምርምር ስራዎች ጥራት ላይ ያተኮረ ስልጠና ለዘርፉ ባለሙያዎች እና ተመራማሪዎች በኦሮሞ ባህል ማዕከል እየተሰጠ ነው።

‎የሚካሄዱት ምርምሮች እና ጥናቶች ሳይንሳዊ እና በእውቀት ላይ የተመሰረቱ መሆን እንደሚገባቸው የኦሮሞ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ አስራት ገልጸዋል ።

‎ኢንስቲትዩቱ በኦሮሞ ሕዝብ ላይ ያተኮረ 73 ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ጥናቶች እና ምርምሮች እየተካሄዱ መሆኑን አቶ ዝናቡ ተናግረዋል ።

‎የምርምር ስራዎች በጋራ ትርክት ላይ የሚያተኩር እና በጋራ መቆም የሚያስችሉ ጉዳዮችን ያካተተ መሆኑንም ገልጸዋል ።

‎የሚካሄዱ ማንኛውም የምርመራ ስራዎች ደረጃቸውን የጠበቁ የምርምር ስራዎች መሆን እንደሚገባቸው የተናገሩት ደግሞ የኦሮሚያ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ ደራራ ከተማ (ረ/ፕ) ናቸው ።

‎የኦሮሞን ባህል ፣ ኪነ ጥበብ እና ማንኛውም የምርመራ እና የጥናት ውጤቶች በአለም አቀፍ ቋንቋ ለአለም አቅፍ ማህበረሰብ ተደራሽ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑንም ተናግረዋል ።

‎የምርምር ስራዎች ለአንድ ችግር መፍትሄ በማመላከት ረገድ ትልቅ ሚና እንዳላቸዉ የገለፁት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቋንቋና ስነ- ፅሁፍ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ታደሰ ጃለታ ( ዶ/ር ) የምርምር ስራ በምርምር ሂደት በዉስጡ በርካታ ሳይንሳዊ ሂደቶችንና ግብዓቶችን ማካተት እንዳለበት ተናግረዋል።

‎በዳንኤል መላኩ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review