በስልጠና ላይ የሚገኙ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በቦራ ወረዳ የፓፓያ ክላስተርን ጎበኙ

You are currently viewing በስልጠና ላይ የሚገኙ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በቦራ ወረዳ የፓፓያ ክላስተርን ጎበኙ

AMN ጥቅምት 28/2018 ዓ.ም

በስልጠና ላይ የሚገኙ የፌደራል : የከተማ እና የተለያዩ ክልሎች ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች በምስራቅ ሸዋ ዞን ቦራ ወረዳ በክላስተር በመልማት ላይ የሚገኝ የፓፓያ ማሳን ጎብኝተዋል።

በክላስተር እየለማ የሚገኘዉ የፓፓያ ዝርያ በዘጠኝ ወራት ዉስጥ ምርት እንደሚሰጥ ሲሆን ልዩ ጣዕም ያለዉና በገበያ ላይ ተፈላጊ መሆኑ ተገልጿል።

ከአንድ የፓፓያ ተክል እስከ አንድ ኩንታል የሚደርስ ምርት እንደሚገኝ ከምስራቅ ሸዋ ዞን ግብርና ጽ/ቤት ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።

በጉብኝቱ ላይ የታደሙ አመራሮችም ያገኙትን ተሞክሮ በአካባቢያቸዉ ለማስፋፋት የሚሰሩ መሆኑን ኦቢኤን ዘግቧል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review