በሃገሪቱ ጠንካራ፣ ዘላቂና እውነተኛ የዲሞክራሲ እና የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ለመገንባት የፖለቲካ ፓርቲዎች ከፍተኛ ድርሻ አላቸው

You are currently viewing በሃገሪቱ ጠንካራ፣ ዘላቂና እውነተኛ የዲሞክራሲ እና የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ለመገንባት የፖለቲካ ፓርቲዎች ከፍተኛ ድርሻ አላቸው
  • Post category:ፖለቲካ

AMN ህዳር 6/2018

የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሕግና ስርዓትን ተከትሎ ለመስራት የሚያስችል የመተዳደሪያ ደንብ ላይ ሰልጠና እየሰጠ ነው።

በስልጠና መድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አዲስ መሃመድ በሀገሪቱ ጠንካራ፣ ዘላቂና እውነተኛ የዲሞክራሲ እና የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ለመገንባት የፖለቲካ ፓርቲዎች ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ገልጸዋል።

በመሆኑም ይህ ሚናቸው እንዲሳካ ለተለያዩ የምክር ቤቱ አደረጃጀቶች የጋራ ምክር ቤቱ የመተዳደሪያ ደንብ ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን አመላክተዋል።

ስልጠናው የጋራ ምክር ቤቱ ተግባርና ኃላፊነት እና ሕግና ስርዓትን ተከትሎ ባለመሰራቱ ሊከሰት የሚችሉ የስነ ምግባር ጉድለቶችን ለማረም የሚረዳ መሆኑ ተነስቷል ።

የጋራ የምክር ቤቱ አባላት ከስልጠናው በኃላ አዲስ ሞሶብን እና አራዳ ፓርክን ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል ።

በዳንኤል መላኩ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review