25ኛው የሶፊ ማልት የታላቁ ሩጫ በኢትዮጰያ በስኬት ተጠናቋል

You are currently viewing 25ኛው የሶፊ ማልት የታላቁ ሩጫ በኢትዮጰያ በስኬት ተጠናቋል

AMN ህዳር 14 ቀን 2018 ዓ/

‎25ኛው የሶፊ ማልት የታላቁ ሩጫ በኢትዮጰያ በስኬት መጠናቀቁ የአዲስ አባባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡

‎መነሻና መዳረሻውን መስቀል አደባባይ በማድረግ የተካሄደው 25ኛው የሶፈ ማልት ታላቁ ሩጫ ውድድር በስኬት መጠናቀቁን የአዲስ አባባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ለኤ ኤም ኤን በላከው መግለጫ አሳውቋል

‎ መምሪያው የውጭ ሀገር ዜጎች ፣ አምባሳደሮች ፣ ታዋቂ ሰዎች እና በርካታ ህዝብ የታደሙበት ከተማችን አዲስ አበባ ለ25ኛ ጊዜ ያስተናገደችው ሩጫ በስኬት ተጠናቋል ብሏል፡፡

‎ ፖሊስ መምሪያው ፕሮግራሙ በአግባቡ እንዲከናወን የፀጥታ ተቋማት ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት አድርገው ወደ ስራ በመግባታቸው እና በያዝነው ዓመት ህዝብ በስፋት የታደመባቸው ልዩ ልዩ ሁነቶች በስኬት መጠናቀቁን አስታውሷል።

‎የዘንድሮው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ሩጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርቧል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review