የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዜጎችን የቤት ባለቤት ለማድረግና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል

You are currently viewing የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዜጎችን የቤት ባለቤት ለማድረግና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል

AMN ህዳር 16 / 2018 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤት አቅርቦት ችግርን ለመፍታት በመንግስት ፣ በበጎ ፈቃድ (ኢኒሼቲቭ) እና በግል ገንቢዎች (አልሚዎች) ትብብር በርካታ ቤቶችን በመገንባት በፍትሐዊነት ዜጎችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው፡፡

በዚህም በተለያዩ አማራጮች ቤቶችን በመገንባት፣ የመኖሪያ ቤት አቅርቦትን በማሻሻል አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግቧል፡፡

አስተዳደሩ ከግል ባሀብቶች ጋር በቅንጅት በመስራት፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የዜጎችን የቤት ፍላጎት ለማሟላትና ተደራሽ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡

እስካሁን ድረስ በተለያዩ ፕሮግራሞች የተከናወነው ዝርዝር የሚከተለው ነው፦

👉 በኮንዶሚኒየም ፕሮግራም:- 139,008

👉 ለአቅመ ደካሞች እና ለአገር ባለዉለታዎች (በመንግስት እና በበጎ ፈቃደኞች ትብብር የተገነቡ):- 40,576

👉 በከተማ አስተዳደር ለኪራይ የተገነቡ:- 24,819

👉 በሪል እስቴት፣ በማህበር እና በግል ገንቢዎች የተገነቡ:- 175,605

👉 በድምሩ ከ380,000 በላይ የሚሆኑ ቤቶችን ለተጠቃሚዎች አስተላልፏል፡፡

በቀጣይም የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ጥያቄ ለመመለስ በትኩረት የሚሰራ ይሆናል፡፡ – የከንቲባ ጽ/ቤት

#Ethiopia

#addisababa

#housing

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review