የአዲስ አበባ ከተማን ሰላም አስተማማኝ ለማድረግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል

You are currently viewing የአዲስ አበባ ከተማን ሰላም አስተማማኝ ለማድረግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል

AMN ህዳር 18/2018

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ከሞተር ሳይክል ማህበር አባላት ጋር ወንጀል መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ ለሁለተኛ ዙር ውይይት አካሃዷል።

ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ተስፋዬ ደንድር የአዲስ አበባ ሰላም አስተማማኝ ለማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ ስለመሆኑ አንስተዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ በሞተር ሳይክል የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመከላከል በትብብር እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ምክትል ኃላፊው ወንጀል ፈፅመው በተገኙት ላይም ርምጃ እየተወሰደ ነው ብለዋል።

በቀጣይም የከተማዋን ሰላም ለማደናቀፍ በሚሰሩት ላይም የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ሞተር ሳይክሎችን ለስራ ብቻ በማዋል በሞተር ሳይክል የሚፈፀሙ ወንጀሎችን መከላከል እንደሚገባም አቶ ተስፋዬ ገልፀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በትብብር መመካከርና መወያየት አስፈላጊ በመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረጉ ውይይቶች በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተመላክቷል።

በፅዮን ማሞ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review