ኢትዮጵያ መልከ ብዙ መሆኗን በመረዳት የጋራ ትርክትን በማስረፅ ለልማት እና ለእድገት መስራት ይገባል

You are currently viewing ኢትዮጵያ መልከ ብዙ መሆኗን በመረዳት የጋራ ትርክትን በማስረፅ ለልማት እና ለእድገት መስራት ይገባል
  • Post category:ወቅታዊ

‎AMN ሕዳር 28/2018 ዓ.ም

‎ኢትዮጵያ መልከ ብዙ መሆኗን በመረዳት የጋራ ትርክትን በማስረፅ ለልማት እና ለእድገት መስራት እንደሚገባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ተናገሩ።

‎ ይህንን የተናገሩት 20ኛውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን አስመልክቶ በተዘጋጀው ሲምፖዚየም ላይ ሲሆን፣ ትልቁ ሀገራዊ ፈተና ብዝሀነት እያወቁ ተግባራዊ ለማድረግ አለመፈለግ መሆኑን አብራርተዋል።

በ‎ሲምፖዚየሙ በበርካታ ወሳኝ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል።

‎በውይይቱ ወቅት “ዴሞክራሲና የፌዴራል ስርዓት”፣ “የምርጫ ስርዓት”፣ “ብዝሐነትና የብዝሐነት አስተዳደር” እንዲሁም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ብዝሐነትና ፀጋን የዳሰሱ ጥናታዊ ፅሑፎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ፣ ሀገራዊ አንድነትን ለማስጠበቅ እና ልማትን ለማረጋገጥ በሀገራዊ የጋራ ትርክት ላይ በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል።

‎የሲምፖዚየሙ ሌላኛው ተሳታፊ የሆኑት አረጋዊ በርሄ ዶ/ር ደግሞ ሰላምና አንድነትን ለማስፈን በዴሞክራሲያዊ መግባባት መስራት እንደሚገባና ህዝቦች በአንድነት ሊቆሙ እንደሚገባ ተናግረዋል።

‎ከዚህ ቀደም የብሔሮች በዓል ይከበር እንደነበር ጠቅሰው፣ አሁን ግን በዓሉ ትርጉም ባለው መልኩና ፍትሀዊ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ ሁኔታ መከበሩ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ እያገኘ መሆኑን እንደሚያሳይ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

‎ይህንን አዎንታዊ እንቅስቃሴ አጠናክሮ ማስቀጠል ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር ብልፅግናን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን አስምረውበታል።

‎‎‎ ኢትዮጵያን “እንደ ጃንጥላ” አድርገው በመመሰል ያስረዱት ተሳታፊዎቹ፣ ሁሉም የጃንጥላው ክፍል የሆኑ ብሔሮችና ብሔረሰቦች የራሳቸውን ማንነት ከሀገር አንድነት ጋር አዛምደውና አጋምደው ማስቀጠል እንዳለባቸው አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

‎በመሆኑም፣ ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር ብልፅግናን ማረጋገጥ የሁሉም ዜጋ ግዴታ መሆኑ በሲምፖዚየሙ ላይ የተሰነዘረ ዋና መልዕክት ነበር።

‎በያለው ጌታነህ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review