‎”አዲስ አበባ አስደማሚ እድገት እያስመዘገበች መሆኑን አይቻለሁ” – የአፍሪካ ሚዲያ አዋርድ ዳኛ አያንዳ ሆሎ

You are currently viewing ‎”አዲስ አበባ አስደማሚ እድገት እያስመዘገበች መሆኑን አይቻለሁ” – የአፍሪካ ሚዲያ አዋርድ ዳኛ አያንዳ ሆሎ

‎AMN – ታሕሳስ 02/2018 ዓ.ም

‎ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ድል ያስመዘገቡት ድል በሁሉም ፈተናዎች እንደማይሸነፉና ፅናት እንዳላቸው ምርጥ ማሳያ መሆኑን መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደረገው የብሪክስ የቴሌቪዥን ጣቢያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ሚዲያ አዋርድ ዳኛ የነበሩት አያንዳ ሆሎ ተናገሩ፡፡

‎‎ሰሞኑን በአዲስ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ በተካሄደው የአፍሪካ ሚዲያ አዋርድ ዳኛ የነበሩት የደቡብ አፍሪካዊ አያንዳ ሆሎ፤ ከዚህ ቀደም የአፍሪካ ህብረት ጉባኤን ለመዘገብ ወደ አዲስ አበባ ተመላልሰዋል፡፡

‎አያንዳ ሆሎ ወደ አዲስ አበባ በመጣሁ ጊዜ ከተማዋ ሁሌም አስደማሚ እድገት እያስመዘገበች መሆኑን አይቻለሁ ብለዋል ::

‎‎በከተማዋ በሁሉም ቦታዎች የህንፃዎችና የተለያዩ መሰረተ ልማት ግንባታዎች እየተካሄዱና ከተማዋ በከፍተኛ ደረጃ እያደገች እንደምትገኝም መመልከታቸውን ገልጸዋል፡፡

‎‎ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብት የታደለች፤ በፈጠሪ ዘንድም የተባረከች ሀገር ናት ያሉት አያንዳ ሆሎ፤ ኢትዮጵያውያን ወራሪውን ፋሺስት ጣሊያንን በማሸነፍ በዓድዋ ጦርነት ያስመዘገቡት ድል በሁሉም ፈተናዎች እንደማይሸነፉና ፅናት እንዳላቸው ማሳያ ስለመሆኑ ጠቁመዋል፡፡

‎‎ኢትዮጵያውያን ከዓድዋ ድል ስኬት፤ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት እስከ የአፍሪካ ህብረት ምስረታ ለአፍሪካ ዘርፈ ብዙ አበርክቶ ያላት ሀገር በመሆኗ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ መሆኗ ትክክለኛ ውሳኔ ነው፤ ይገባታልም ብለዋል፡፡

‎‎የዓድዋ ድል የኢትዮጵያውያን ድል ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ የነፃነት እርሾ ምንጭ በሆነችው በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የአፍሪካ ሚዲያ አዋርድ መካሄዱ ሌሎችንም የሚያነቃቃ መሆኑን አንስተዋል፡፡

‎‎ኢትዮጵያ ለቀደሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ኔልሰን ማንዴላ ስልጠና በመስጠት ደቡብ አፍሪካን ከአፓርታይድ አገዛዝ ስርዓት ነፃ እንድትሆን ታሪካዊ ድጋፍ ማድረግ መቻሏንም ጠቁመዋል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review