የኪነ – ጥበብ ፈጠራ ስራዎች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ሊያስጠብቁ ይገባል

You are currently viewing የኪነ – ጥበብ ፈጠራ ስራዎች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ሊያስጠብቁ ይገባል

AMN – ታሕሳስ 4/2018 ዓ.ም.

የኪነ – ጥበብ ፈጠራ ስራዎች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ሊያስጠብቁ እንደሚገባ ተገለጸ።

በኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር የማሕበራዊ ጉዳይ አማካሪ ሚኒስትር ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የኪ – ጥበብ ስራዎች የኢትዮጵያን ብሄራዊ ጥቅም ለማስከበር እና በሀገር ጉዳይ በጋራ ለመቆም ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል፡፡

ከክልል እና ከፌዴራል የተውጣጡ የኪነ – ጥበብ ፈጠራ ባለሙያዎች፣ የክልል የባህል እና በኪነ – ጥበብ ዘርፍ ኃላፊዎች በአፍሪካ የአመራር ልህቀት አካዳሚ በኪነ – ጥበብ ፈጠራ ስራዎች እና ብሄራዊ ጥቅምን በተመለከተ ሰነድ ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበት ይጠበቃል፡፡

የኪነ ጥበብና ስነ ጥበብ ፈጠራዎች የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም የሚያረጋግጡ መሆኑ ይገባቸዋል ብለዋል።

ሀገር አንድ ናት ፣ ፓርቲዎች ብዙ ናቸው ፣ ሁላችንም እናልፋለን በመሆኑም ሀገር ይቀጥላል የኪነ ጥበብ ስራዎች በሙሉ የሀገርን አንድነት እና ሕብረት መጠበቅ አለባቸው ሲሉ ተናግረዋል ሚኒስትር ድኤታው።

አዲስ ሲኒማ ማዕከል ፣ ኮፊ ፓርክ ፣ አራዳ ፓርክን እና ሙያ ኢትዮጵያ የዕደ ጥበብ ስራዎች ማምረቻ ማህበርን እና በእንጦጦ የሚገኘውን የሰርከስ ሴንተር ከክልል እና ከፌዴራል የተውጣጡ የኪነ – ጥበብ ባለሙያዎች እና የክልል የባህል እና የኪነጥበብ ዘርፍ ኃላፊዎች መጎብታቸው ይታወሳል ።

በዳንኤል መላኩ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review