ውይይቱ ሀገራዊ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችል ነው

You are currently viewing ውይይቱ ሀገራዊ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችል ነው
  • Post category:ፖለቲካ

‎AMN ታህሳስ 4/2018ዓ.ም

‎”የጉባ ብስራቶች፣ የመደመር መንግስሥት ትሩፋቶች!” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ የሚገኘው ሕዝባዊ ውይይት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳደርም ቀጥሏል።

‎ውይይቱ በሐገር ሽማግሌዎች የሐይማኖት አባቶች እና አባ ገዳዎችና ሀደ ስንቄዎች በፀሎትና በምስጋና ተከፍቷል።

‎በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ የጉለሌ እፅዋት ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ጉተማ ሞረዳ (ኢ/ር) ፣ውይይቱ ሀገራዊ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችል ነው ብለዋል።

‎ ከዚህ ቀደም አስተዳደሩ መሰል ሕዝባዊ ውይይቶች ሲያካሂድ የቆየ መሆኑን አስታውሰው፣ መድረኩ ተለዋዋጭ በሆነው ሀገራዊ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑንም ገልፀዋል።

‎በአዲስ አበባ ከተማ ከለውጡ ወዲህ በርካታ ሰው ተኮር የልማት ስራዎች መከናወናቸውን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል ።

‎ለዚህም ስኬቶች የከተማ አስተዳደሩ አመራር ከነዋሪው ጋር በጋራ በቅንጅት በመሰራቱ የተመዘገበ ድል መሆኑን አስታውሰዋል።

‎የክፍለ ከተማው የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊና የብልፅግና ፖርቲ ምክትል ኃላፊ አቶ ሲሳይ ኬኔ ሕዝባዊ ውይይቱ ነዋሪው የሚያነሳቸውን ችግሮች በአግባቡ ለመለየት እና

‎ለመፍትሔው አብረን ለመሰሰራት ያስችለናል ብለዋል።

‎በመድረኩ ለውይይት የተዘጋጀ ሰነድ እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን ሰነዱን መነሻ በማድረግ ሰፊ ውይይት እንደሚካሄድ ይጠበቃል።

‎በታምሩ ደምሴ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review