ከንቲባ አዳነች አቤቤ የሃባሪ ሜዲካል ፕላዛን መርቀዉ ስራ አስጀመሩ

You are currently viewing ከንቲባ አዳነች አቤቤ የሃባሪ ሜዲካል ፕላዛን መርቀዉ ስራ አስጀመሩ

AMN ታኅሣሥ 25/2018 ዓ.ም

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልእክት ዛሬ የሃባሪ ሜዲካል ፕላዛን መርቀን በይፋ ሥራ አስጀምረናል ብለዋል፡፡

ተቋሙ ለሀገራችን ጥራት ያለው የሕክምና አማራጭ ይዞ የመጣ ማዕከል ነው። ሃባሪ ሜዲካል ፕላዛ ዜጎች ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚያደርጉትን ጉዞ በማስቀረት፣ ጥራት ያለው አገልግሎት በሀገር ውስጥ ለማቅረብ የጀመረው ጉዞ ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል፡፡

ተቋሙ አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ ለጀመርነው ጉዞ ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር በመሆኑ፣ ሁሉን አቀፍ ድጋፋችን አይለያችሁም።

ለዚህ በጎ ጅምር እና ለላቀ አገልግሎታችሁ ያለኝን አድናቆት እየገለጽኩ፤ ለተቋሙ ስኬታማ የሥራ ዘመን እመኛለሁ ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review