የኦማን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ፀሃፊ ሼክ ካሊፋ ቢን አሊ አል ሃርቲ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ምክትል ፀሃፊዊ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱም በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመካከለኛው ምስራቅ፣ እስያ እና ፓስፊክ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደዋኖ ከድር አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ሼክ ካሊፋ ቢን አሊ አል ሃርቲ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ከተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ይገናኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመልክቷል።