የመጀመሪያው ምዕራፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ሥራ በአመት 60 ሚሊዮን ተጓዦችን የማስተናገድ አቅም አለዉ
ከአዲስ አበባ ደቡብ ምስራቅ 40 ኪሎሜትር አካባቢ በምትገኘውና 1910 ሜትር ከፍታ ባላት ቢሾፍቱ ከተማ ይገነባል
ግንባታዉ ሲጠናቀቅ አፍሪካን ከአለም ቀዳሚ የአየር ትራንስፖርት መነኻሪያዎች አንዷ ያደርጋታል
ሃገሪቱ በአመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ላይ እንድትደርስ ያደርጋል
ቢሾፍቱ ለአውሮፕላኖች ሥራ የተመቸ ከባቢ አላት
መዳረሻቸውን ኢትዮጵያ ላደረጉም ሆነ ለትራንዚት መንገደኞች ብቁ ሁኔታ ያላት ከተማ ናት
በአፍሪካ ታሪክ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ፕሮጀክት ይሆናል
ከነባሩ የአየር ትራንስፖርት ምኅዳር ጋር በቀላሉ የተዋሃደ አሠራር እንዲኖር ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል
ቦሌ አለምአቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ 25 ሚሊዮን የሚጠጉ መንገደኞችን በአመት የማስተናገድ አቅሙ አለዉ
ኢትዮጵያን የወደፊቷ የአፍሪካ ግምባር ቀደም የአየር ትራንስፖርት በር የማድረግ አላማን ያነገበ ነው
ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ሪፎርም፣ የኢንደስትሪ ማስፋፊያ አጀንዳ እና የረጅም ዘመን የአቪየሽን ስትራቴጂ ጋር የተናበበ ነው
ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድን አለምአቀፍ ተወዳዳሪነት ያጠናክራል
በAfCFTA ማህቀፍ የአፍሪካን የማገናኘት አቅም ይጨምራል
የንግድ እና ቱሪዝም ኮሪደሮችን ያሰፋል
ኢትዮጵያንም ቀዳሚ የበይነ አኅጉር ማዕከል ያደርጋታል