የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ከ12 ሀገራት የተውጣጡ 457 የአቪዬሽን ባለሙያዎችን አስመረቀ።
በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰውን ጨምሮ የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች እና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል፡፡
ከተመራቂዎቹ ውስጥ 58 ፓይለቶች፣ 115 የአውሮፕላን ጥገና ቴክኒሻኖች እና 284 የበረራ አስተናጋጆች መሆናቸዉን ከአየር መንገዱ ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል፡፡