AMN ጥር 20 ቀን 2018 ዓ.ም
የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የሊግ ምዕራፍ ጨዋታዎች ሲጠናቀቁ ወደ ጥሎ ማለፍ በቀጥታ ካለፉ ስምንት ክለቦች አምስቱ ከእንግሊዝ ሆነዋል።
ስምንቱንም ጨዋታዎች አሸንፎ ታሪክ የሰራው አርሰናል ፣ ሊቨርፑል ፣ ቶተንሃም ፣ ቼልሲ እና ማንችስተር ሲቲ በቀጥታ ያለፉ የእንግሊዝ ክለቦች ናቸው።
ባየርን ሙኒክ ፣ ባርሰሎና እና የፖርቹጋሉ ስፖርቲንግ ሊዝበን ሌሎች በቀጥታ ያለፉ ክለቦች ናቸው።
በውድድሩ ከ9-24 ያጠናቀቁ ክለቦች የእርስ በእርስ ጨዋታ አከናውነው አሸናፊ ስምንት ክለቦች በቀጥታ ካለፉ ስምንት ክለቦች ጋር የሚፋለሙ ይሆናል።
የባለፈው ዓመት የውድድሩ አሸናፊ ፓሪሰን ዠርማ ፣ ሪያል ማድሪድ ፣ ኢንተር ሚላን ጁቬንቱስ እና አትሌቲኮ ማድሪድ ለቀጣይ ጨዋታ ከሚዘጋጁ ክለቦች መሀከል ይጠቀሳሉ። ዕጣ ድልድሉ የፊታችን አርብ ይከናወናል።
ከ25-36 ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁ ክለቦች ደግሞ ከውድድሩ ውጪ ሆነዋል።
ናፖሊ ፣ ማርሴይ ፣ አትሌቲክ ቢልባኦ ፣ አያክስ እና ቪያሪያል ከውድድሩ ውጪ ከሆኑ ክለቦች መሀከል ይጠቀሳሉ።
በሸዋንግዛው ግርማ።